ҽ

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ እና የአሜሪካ የካቶሊክ ጳጳሳት ጉባኤ ሊቀ ጳጳስ ቲሞቴዎስ ብሮሊዮ በቫቲካን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ እና የአሜሪካ የካቶሊክ ጳጳሳት ጉባኤ ሊቀ ጳጳስ ቲሞቴዎስ ብሮሊዮ በቫቲካን   (Vatican Media)

ሊቀ ጳጳስ ብሮሊዮ ለርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ መልእክት ምስጋናቸውን መግለጻቸው ተገለጸ

ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ለስደተኞች የምያደርጉትን ድጋፍ አስመልክቶ ለአሜሪካ ጳጳሳት የላኩትን መልእክት ተከትሎ የአሜሪካ የካቶሊክ ጳጳሳት ጉባኤ ሊቀ ጳጳስ ቲሞቴዎስ ብሮሊዮ፣ እጅግ ለተቸገሩት ሰዎች የምያደርጉትን ሐዋርያዊ እንክብካቤ ሥራቸውን እንዲቀጥሉ ላቀረቡት የማበረታቻ መልእክት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስን አመስገነዋል።

የዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ-ቫቲካን

"የሰውን ሁሉ ክብር የጠበቀ ማህበረሰቦቻችንን ለመገንባት ሰብዓዊ የሆነ ስርዓቱን የጠበቀ የስደተኞች ሕግ እንዲኖር እንደ ሀገር ድፍረት እንድናገኝ ቀጣይ ፀሎታችሁን እጠይቃለሁ" ብለዋል።

የአሜሪካ የካቶሊክ ጳጳሳት ጉባኤ (USCCB) ዋና ጸኃፊ የሆኑት ሊቀ ጳጳስ ቲሞቲ ብሮሊዮ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ ለአሜሪካ ጳጳሳት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ በላኩት ስደተኞችን የተመለከተ መልእክት የምስጋና ደብዳቤ ላይ ይህንኑ ገልጸዋል።

ለሁሉም ተስፋ የሚሰጥ መልእክት ነው

“የቅዱስ ጴጥሮስ ተተኪ እንደመሆኖ መጠን፣ እያንዳንዱን ካቶሊክ ብቻ ሳይሆን እያንዳንዱን ክርስቲያን በእምነት አንድ የሚያደርገንን ነገር እንድታከናውኑ ተጠርታችኋል —ለእያንዳንዱ ሰው፣ ዜጋ እና መጤ የኢየሱስ ክርስቶስን ተስፋ አቅርቡ” ሲሉ አመስግኗል።

የአሜሪካ ጳጳሳት ጉባኤ ፕሬዘዳንት "በእነዚህ የፍርሀት እና የግራ መጋባት ጊዜዎች፣ ለአዳኛችን 'ለእነዚህ ከታናናሾቻችን ለአንዱ ምን አደረክ?' የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ ዝግጁ መሆን አለብን" ብለዋል።

ተስፋ የቆረጡ ሰዎችን መርዳት

ከዚህም በላይ ሊቀ ጳጳስ ብሮሊዮ "ድንገተኛ ዕርዳታ በመቋረጡ የሚሰቃዩ ቤተሰቦች ለመጽናት የሚያስችል ጥንካሬ እንዲያገኙ" ወደ ጌታ እንዲጸልዩ ምእመናን ሁሉ እንዲተባበሩ የጋበዙ ሲሆን የአሜሪካው ሊቀ ጳጳስ፣ “ከአንተ ጋር፣ የአሜሪካ መንግሥት ተስፋ የቆረጡ ሰዎችን ለመርዳት የገባውን ቃል እንዲጠብቅ እንጸልያለን" ብለዋል።

የአሜሪካ ጳጳሳት ጉባኤ ፕሬዝደንት በደብዳቤያቸው ላይ የካቶሊክ የእርዳታ አገልግሎቶችን ብሔራዊ ስብስብ ይህንን በሚቀጥለው ጊዜያት የምጀመረውን የዐርባ ጾም ወቅት ምጽዋት በመስጠት በመደገፍ እንዲሁም በአካባቢው የካቶሊክ በጎ አድራጎት ድርጅቶች “ክፍተቱን በሁሉም ጥረት እንዲሞላ” ከእግዚአብሔር ሕዝብ ምሕረትና ልግስና ጠይቀዋል።

"በመካከላችን ለችግረኞች የምናደርገውን እንክብካቤ ለመቀጠል ስንታገል እና ስደተኞች ወደ ባህር ዳርቻችን በሚመጡባቸው ቦታዎች ያለውን ሁኔታ ለማሻሻል ፍላጎታችን ነው" ሲል አጉልቶ ተናግሯል "በእነርሱ ውስጥ የክርስቶስን ፊት እንደምናይ ሁልጊዜ እናስታውሳለን" ብለዋል።

በዚህ የኢዮቤልዩ ዓመት ሊቀ ጳጳስ ብሮሊዮ "የእርቅ፣ የአንድነት እና የወንድማማችነት ድልድይ እንገንባ" በማለት ከገለጹ በኋላ ምልእክታቸውን አጠናቀዋል።

14 Feb 2025, 16:37